Fana: At a Speed of Life!

ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ በኢትዮጵያ ከቱርክ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 16 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ (ኢ/ር) በኢትዮጵያ ከቱርክ አምባሳደር ቤርክ ባራን ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ የቱርክ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ተመራጭ ባደረጓቸው የኢንቨስትመንት እድልና አማራጮች ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።

ከዚህ ባለፈም የጋራ የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ዘርፍ የማስተዋወቅ ስራ ላይ ያተኮረ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.