Fana: At a Speed of Life!

ወልቂጤ ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 21 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ26ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ወልቂጤ ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድንን ያስተናገደው ወልቂጤ ከነማ 2 ለ 0 ማሸነፍ ችሏል፡፡

የወልቂጤ የማሸነፊያ ጎሎችን በእለቱ ድንቅ ብቃቱን ያሳየው ጌታነህ ከበደ በፍፁም ቅጣት ምት እና በጨዋታ ማስቆጠር ችሏል፡፡

በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕናን የገጠመው ኢትዮጵያ ቡና 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል፡፡

አማኑኤል ዮሀንስ እና መስፍን ታፈሰ የኢትዮጵያ ቡና የድል ግቦች ያስቆጠሩ ሲሆን ባየ ገዛኸኝ የሃድያ ሆሳና ን ብቸኛ ጎል አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተክትሎ ቡናማዎቹ ደረጃቸውን ያሻሻሉ ሲሆን ነጥባቸውን 38 በማድረስ 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመት ችለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.