በሰሞኑ ዝናብ ቦረና ላይ በስፋት የእንስሳት መኖ እና ሰሊጥ ተመርቷል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሞኑ ዝናብ ቦረና ላይ በስፋት የእንስሳት መኖ እና ሰሊጥ ተመርቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት እንደገለፁት÷ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ከድርቅ ወደ አምራችነት መቀየሩ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
ውኃን በማቆርና በመቆጠብ ብልሐት ከተጠቀምን የችግርን ጊዜ ሳንቸገርበት እናልፈዋለን ሲሉም ነው የገለፁት።