አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንቼስተር ሲቲ የከተማ ተቀናቃኙን ማንቼስተር ዩናይትድ በማሸነፍ የእንግሊዝ ኤፍ ኤፕ ካፕ ዋንጫን አሸንፏል።
11 ሰዓት ላይ በተካሄደው የማንቹሪያ ደርቢ የፍፃሜ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በጀርመናዊዉ አጥቂ ኤልካይ ጎንዶጋን ጎሎች 2 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫውን ከፍ አድርገዋል።
ሦስትዮሽ የዋንጫ ጉዟቸውን የቀጠሉት ስፔናዊው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ከውሃ ሰማያዊዎቹ ጋር ሁለተኛ የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫቸውን ማንሳት ችለዋል።
ሲትዝኖቹ የውድድር ዓመቱን ሁለተኛ ዋንጫ ካዘናቸው ውስጥ ያስገቡ ሲሆን ፥ ሦስተኛ ዋንጫቸውን ለማገኘት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ከኢንተርሚላን ጋር ለመፋለም ቀጠሮ ይዘዋል።
በሚኪያስ አየለ
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!