Fana: At a Speed of Life!

200 የኩባ ሐኪሞች  የኮሮና ቫይረስን ለመዋጋት ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊያቀኑ ነው

አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 18፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ደቡብ አፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመዋጋት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ 200 የሚሆኑ የኩባ ሀኪሞች ወደ ሀገሪቱ ሊያቀኑ መሆኑ ተሰምቷል።

ዶክተሮቹ ደቡብ አፍሪካ  ከደረሱ በኋላም  በሀገሪቱ  ወደ ሚገኙ የተለያዩ ክልሎች  እንደሚሰማሩም ነው የተነገረው።

ሀኪሞቹ ኮቪድ -19ን ለመዋጋት  ኩባን እርዳታ ለጠየቁ  22 አገሮች   ከተላኩ 1 ሺህ  200የጤና እንክብካቤ ሠራተኞች ውስጥ  የሚካተቱ ናቸውም ነው የተባለው፡፡

ደቡብ አፍሪካ ወረርሽኙን ለመከላከል በመላው ሀገሪቱ  ጥላው የነበረውን ጥብቅ የእንቅስቃሴ ገደብ ከሚቀጥለው ወር  ጀምሮ ማላላት እንደምትጀምር ተገልጿል፡፡

በዚህም ከ 1ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ወደ ሥራ እንዲመለሱ  የሚፈቀድላቸው ይሆናል ተብሏል።

ከዚያም ባለፈ አንዳንድ ትምህርት ቤቶች እንደገና  የሚከፈቱ ሲሆን ትኩስ የምግብ አቅርቦት እና ሲጋራዎች እንዲሸጡ ይፈቀዳል ነው የተባለው፡፡

ነገር ግን የአልኮል ሽያጭና እና የሕዝብ ስብሰባዎች እንደታገዱ  እንደሚቆዩ ተነግሯል።

በደቡብ አፍሪካ እስካሁን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ 4 ሺህ 361   ሰዎችን  የተያዙ ሲሆን 86 የሚሆኑትን ደግሞ ለህልፈት ዳርጓል።

ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.