Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች ከተለያዩ ሃይማኖት መሪዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከሁሉም የእምነት ተቋማት ከተውጣጡ የሃይማኖት መሪዎች እና ከሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አመራሮች ጋር ተወያዩ፡፡

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ÷ ማምሻውን ከሁሉም የእምነት ተቋማት የሃይማኖት መሪዎች እና ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች ጋር ገንቢ ውይይት አድርገናል ብለዋል፡፡

“በውይይታችንም÷ ሰላምን ለማፅናት በቁርጠኝነት በትብብር መስራት እንዳለብን ተስማምተናል” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

“በኃይማኖቶች መካከል ያለውን ቅርበት እና ትብብር  ማጠናከር ሰላምን ከማፅናት ባለፈ ለጀመርነዉ ልማትም አስፈላጊ በመሆኑ ይህንኑ አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናልም” ነው ያሉት፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.