Fana: At a Speed of Life!

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ ሲደረግባቸው ለቆዩ 4 ግለሰቦች የዋስትና መብት ተፈቀደ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ ሲደረግባቸው የቆዩ አራት ግለሰቦች የዋስትና መብት ተፈቀደላቸው።

የዋስትና መብት የተፈቀደላቸው ግለሰቦችም ÷ ቴድሮስ አስፋው ፣ ሳሮን ቀባው ፣ ጌታቸው ወርቄ እና ጌታዎይ አለሙ ናቸው።

የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ-ኅግ ÷ በተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ የቀጠለ ቢሆንም ዋስትና ቢፈቀድላቸው እንደማይቃወም አመልክቷል።

በዚህም መሠረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ÷ ለሳሮን ቀባው የ3 ሺህ ብር ፣ ለቴድሮስ አስፋው የ15 ሺህ ብር እንዲሁም ጌታቸው ወርቄ እና ጌታዎይ አለሙ እያንዳንዳቸው የ10 ሺህ ብር ዋስ አስይዘው ከእሥር እንዲፈቱ አዝዟል።

ዐቃቤ-ኅግ በአጠቃላይ 51 በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ክስ የመሰረተ ሲሆን ÷ 24 ተጠርጣሪዎች ላይ ባሉበት፤ በቀሪዎቹ 27 ተጠርጣሪዎች ላይ ደግሞ በሌሉበት ነው ክስ የመሰረተባቸው።

በታሪክ አዱኛ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.