Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ፍጹም አረጋ ከካናዳ የትራንስፖርት ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

 

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 2 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በካናዳ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ ከካናዳ የትራንስፖርት ሚኒስትር እና የፓርላማ አባል ዑመር አልጀብራ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም የበረራ ግንኙነቶችን ማሻሻል በሀገራቱ ብሎም በሁለቱ በአህጉራት መካከል የንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም እና የባህል ልውውጥን ከማሳደግ አንጻር ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ መክረዋል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ከኢትዮጵያ ካናዳ የሚያደርገውን በረራ ማስፋት በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ቶሮንቶ በረራ ያደርጋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.