የሀገር ውስጥ ዜና

የኮሮና ቫይረስና አንበጣ ወረርሽኝ ተጽእኖ የ8 በመቶ የምርት ቅናሽ ሊያሳይ ይችላል- የግብርና ሚኒስቴር

By Tibebu Kebede

April 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የግበርናው ክፍለ ኢኮኖሚ አሁን በተከሰተው የኮሮና ቫየረስና የአንበጣ ወረርሽኝ በጋራ በሚፈጥሩት ተጽእኖ የ8 በመቶ የምርት ቅናሽ ሊያሳይ እንደሚችል የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስቴር የሰብል ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አታ ሳኒ ረዲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ በተለይ ይህ የምርት ቅነሳ ሊያጋጥም የሚችለው በበልግ ወቅት፣ በበጋ መስኖ እና በመኸር ወቅት መሆኑን ገልጸዋል።