Fana: At a Speed of Life!

የተባበሩት መንግሥታት ሥነ ሕዝብ ፈንድ በአፋር ክልል የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያሳድግ ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ከተባበሩት መንግሥታት ሥነ ሕዝብ ፈንድ (ዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ) የኢትዮጵያ ዋና ተጠሪ ካፊ ኩዋሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ ለአፋር ክልል የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል በሚችልበት አግባብ ላይ መክረዋል፡፡

ተቋሙ የክልሉ የስነ ተዋልዶ እና የእናቶችን ጤና ለማሻሻል እንዲሁም ለአቅመ ደካማ ሴቶች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠሉ ተመላክቷል፡፡

ካፊ ኩዋሜ ÷የተባበሩት መንግሥታት ሥነ ሕዝብ ፈንድ ለአፋር ክልል የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያሳድግ ቃል ገብተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በበኩላቸው÷ ተቋሙ እስካሁን ለአፋር ክልል ላደረገው ዘርፈ ብዙ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

 

 

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.