ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር የኢትዮጵያ ተወካይን አሰናበቱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የአገልግሎት ጊዜያቸውን የጨረሱትን የተባበሩትመንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር የኢትዮጵያ ተወካይ ማማዶ ዲያን ባልድን አሰናበቱ።
ማማዶ ዲያን ባልድ በቆይታቸው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ፕሬዚዳንቷ ምስጋና ማቅረባቸውንም የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡