የሀገር ውስጥ ዜና

ጀርመን ለኢትዮጵያ የ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የድጋፍ ማዕቀፍ ይፋ አደረገች

By Tibebu Kebede

April 30, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጀርመን ለኢትዮጵያ የ4 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የድጋፍ ማዕቀፍ ይፋ ማድረጓን የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ሚኒስትር ጀርድ ሙለር አስታወቁ።

የኢኮኖሚ ትብብርና ልማት ሚኒስትር ጀርድ ሙለር፥ ጀርመን በዚህ አስቸጋሪ በሆነው ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት ከኢትዮጵያ ጎን በመሆን አጋርነቷን የምታሳይ መሆኑን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አይመድ ገልፀዋል።