አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው ሰዎች ውስጥ አብዛኞቹ በለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበሩ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ገለፀ።
ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው 131 ሰዎች መሆናቸውን የጠቀሰው ኢኒስቲትዩቱ፥ ከእነዚህም 69 ሰዎች ማለትም 53 በመቶ በአስገዳጅ የለይቶ ማቆያ ከነበሩ መንገደኞች ውስጥ መሆኑ ተረጋግጧል ብሏል።