Fana: At a Speed of Life!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2016 ረቂቅ በጀት ላይ እየመከረ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀምሯል፡፡
ምክር ቤቱ በጉባዔው የ26ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡
በተጨማሪም ምክር ቤቱ የፌደራል መንግሥት የ2016 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ዝርዝር ውይይት እያካሄደ ይገኛል፡፡
በጉባዔው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈጉባዔ ወይዘሮ ሎሚ በዶን ጨምሮ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ እንዲሁም የምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል፡፡

የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በ2016 ረቂቅ በጀት ላይ በቋሚ ኮሚቴውና ከህዝብ የተነሱ ጥያቄዎችን ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡

ለባለበጀት መስሪያ ቤቶች የተደለደለው በጀት ምን ያክል የተቋማትን የመፈጸም አቅም፣ የስራ ስፋት፣ የተቋሙ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ እንዲሁም የኦዲት ግኝት መሰረት ያደረ ምደባ ነው የሚሉ ጥያቄዎች በቋሚ ኮሚቴው ተነስተዋል፡፡

“ምን ያክልስ የወጪ ቁጠባንና ውጤትን መሰረት ያደረገ አመዳደብ ነው?” በሚል ማብራሪያ እንዲሰጥበትም ተጠይቋል፡፡

ከዚህ በፊት በጀት ተይዞላቸው የነበሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች በጀታቸው በሽግሽግ ተነስቶ ግንባታቸው ተጀምሮ የተቋረጠ እንዲሁም ያልተጀመሩ ፕሮጀክቶች እንዳሉም ተጠቅሷል፡፡

በዚህም የ2016 ረቂቅ በጀት እነዚህን ፕሮጀክቶች ታሳቢ ያደረገ እና ቅድሚያ የሰጠ መሆኑ ተረጋግጧል ወይ? ማብራሪያ ቢሰጥበት የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

በየሻምበል ምሕረት
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.