Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ፌዴሬሽን የአስተዳደር ቦርድ አጥኚ ኮሚቴ አባላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የበላይ ጠባቂ ሣኅለወርቅ ዘውዴ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ፌዴሬሽን የአስተዳደር ቦርድ አጥኚ ኮሚቴ አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

የኮሚቴ አባላቱ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

ከጉብኝታቸው በኋላም ከፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ የኢትዮጵያ ቀይመስቀል ማኅበር እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ መክረዋል፡፡

የተጠናከረ ትብብር እና ድጋፍ መደረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይም መወያየታቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.