የሀገር ውስጥ ዜና

የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ የእዳ ስረዛ መከራከሪያ በሎውረንስ ፍሪማን እይታ

By Tibebu Kebede

May 03, 2020

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 25 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ዝቅተኛ ገቢ ያቸው አዳጊ ሀገራትን ከኮቪድ-19 ተፅእኖ ለመጠበቅ እዳቸውን መሰረዝ አስፈላጊ መንገድ መሆኑን ያቀረቡት ሀሳብ ብሄራዊና ዓለም አቀፋዊ ፖሊሲዎች ሊገዙበት የሚገባ መርህ መሆኑን አውቁ የአፍሪካ ጉዳዮች ተንታኙ እና ፀሃፊው ሎውረንስ ፍሪማን ገለፁ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በኒው ዮርክ ታይምስ መፅሄት ላይ ባወጡት ፅሁፍ አበዳሪ ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አዳጊ ሀገራትን ከኮቪድ-19 የከፋ ተፅዕኖ ለመታደግ የብድር መክፈያ ጊዜን ማራዘም ሳይሆን ብድርን መሰረዝ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።