ስፓርት

የ2012 ሁሉም የሊግ ውድድር መሰረዙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ

By Tibebu Kebede

May 05, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የ2012 ሁሉም የሊግ ውድድር መሰረዙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዛሬው እለት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በ2012 ሲካሄዱ በነበሩ አጠቃላይ የሊግ ውድድሮች እጣ ፈንታ ላይ በዛሬው እለት በቴሌ ኮንፈረንስ እና በአካል በፌዴሬሽኑ ጽህፈት ቤት ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።