Fana: At a Speed of Life!

ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የመናኸሪያዎችን አገልግሎት አሰጣጥ ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የመናኸሪያዎችን አገልግሎት አሰጣጥና የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ -19) ወረርሽኝን ለመከላከል እየተሰራ ያለውን ስራ ጎበኙ።

ዛሬ ማለዳ ላይም የአስኮ፣ የመርካቶና የአየር ጤና መናኸሪያዎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም ተገልጋዮችን፣ ሹፌሮችና ሌሎችንም የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከል ስለሚያደርጉት ጥንቃቄና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮችን በተመለከተ ማነጋገራቸውን ኢዜአ አገልግሎት ዘግቧል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማስፈጸም በወጣዉ ድንጋጌ የሚኒስትሮች ኮሚቴ የትራንስፖርት ዘርፍ አፈፃጸም መመሪያ አውጥቶ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.