ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ የፌደራል ፖሊስ ሰራዊት አባላት ተመረቁ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ የፌደራል ፖሊስ ሰራዊት አባላት ዛሬ ተመርቀዋል፡፡
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤልን ጨምሮ የፌደራል እንዲሁም የክልሉ የጸጥታ ተቋማት አመራሮች በተገኙበት ነው የምረቃ ሥነ- ሥርዓቱ የተካሄደው፡፡
አቶ ሙስጠፌ ባደረጉት ንግግር÷ ተመራቂዎቹ በስልጠናው ባገኙት ክህሎት በመታገዝ የተረከቡትን ኃላፊነት በሀገር ወዳድና በፖሊሳዊው ሥነ-ምግባር ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡
በስልጠና ወቅት የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላት እውቅና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል መባሉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!