ቢዝነስ

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች በኢንቨስትመንት ዘርፍ እየተሳተፉ ላሉ አርሶ አደሮችና አነስተኛና ጥቃቅን ማህበራት እውቅና ተሰጠ

By Tibebu Kebede

May 09, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች በኢንቨስትመንት ዘርፍ እየተሳተፉ ላሉ ግንባር ቀደም አርሶ አደሮችና አነስተኛና ጥቃቅን ማህበራት እውቅና ተሰጠ።

የእውቅና ስነስርዓቱ በጅማ ከተማ የተዘጋጀ ሲሆን፥ ከጅማ፣ ቡኖ በደሌና ኢሉ አባቦራ ዞኖች በቡና፣ በእህልና በሻይ ልማት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ተሳትፈውታል።