Fana: At a Speed of Life!

የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ጠንካራ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን የጤና ሚንስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታወቁ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የኮሮና ቫይረስን ከመከላከል አንፃር ጠንካራ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን የጤና ሚንስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ በከተማዋ የኮቪድ19 ወረርሽኝን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በመገኘት ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱም የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የኮሮና ቫይረስን ከመከላከል አንፃር ጠንካራ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ነው ሚንስትሯ የተናገሩት ።

የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል እንዲሁም በተጓዳኝ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም ቡድኑ ጎብኝቷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.