የሀገር ውስጥ ዜና

ዓለም አቀፍ የገንዘብ ዝውውር ስርዓትን በመጠቀም ሊፈፀም የነበረ የ110 ሚሊየን ዶላር የገንዘብ ማጭበርበር እና ዘረፋ ወንጀል ከሸፈ

By Tibebu Kebede

May 10, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ማጭበርበር እና ዘረፋ ወንጀል ማክሸፉን ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።

አገልግሎቱ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ዝውውር ስርዓትን በመጠቀም 110 ሚልዮን ዶላር የማጭበርበርና የዘረፋ የወንጀል ሙከራ በቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ አስታውቋል።