Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የወጪ ንግድ ትስስር ለማሻሻል እየተሰራ ነው – ሚኒስቴሩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የወጪ ንግድ ትስስር ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የቻይና-አፍሪካ የእውቀት ሽግግር ሲምፖዚየም በቻይና ቤጂንግ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

በመድረኩ የተሳተፉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ÷በቻይና የኢትዮጵያ ምርት ገዢ ከሆኑ ታላላቅ የቅባት እህል ተቀባይ ነጋዴዎች ጋር ፍሬያማ ውይይት መደረጉን አንስተዋል፡፡

ቻይና የኢትዮጵያ ወጪ የግብርና ምርቶችን በመቀበል ቀዳሚ መሆኗን ጠቁመው÷ በሀገራቱ ንግድ ልውውጥ ላይ የተስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል፡፡

በሚቀጥሉት ወራት ከቻይና ጋር የሚኖው የወጪ ንግድ መሻሻል እንደሚያሳይ እምነታቸው መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

 

 

 

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.