የሀገር ውስጥ ዜና

በምዕራብ ጎንደር ዞን በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 289 የቱርክ ሽጉጥ እና 2 ባለአንድ እግር ክላሽ ተያዘ

By Tibebu Kebede

May 11, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ)መነሻውን መተማ ወረዳ ኮኪት ቀበሌ ያደረገው መኪና ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ይዞ ሲንቀሳቀስ ተያዘ።

ህገ ወጥ የጦር መሳሪውን የያዘው አይሱዚ የጭነት መኪና ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ እና ጥይት በመጫን በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት ገንዳዉኃ ከተማ መግቢያ ኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ መያዙን ከምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።