አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ሁለተኛ ዙር በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ የቤት ለቤት የኮቪድ-19 አሰሳ ተጀምሯል።
የሁለተኛው በኤሌክትሮኒክስ የተደገፈ የቤት ለቤት የኮቪድ-19 አሰሳ በዋናነት ህብረተሰቡን ማስተማር እና የተገኙ መረጃዎችና ውጤቶች በፍጥነት በማስተላለፍ በሽታውን ለመከላከል የሚደረጉ ጥረቶችን ለማገዝ ከፍተኛ ሚና ሊጫወት እንደሚችል የጤና ሚንስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ተናግረዋል፡፡