ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ብፁዕ አቡነ ሰላማ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ባደረባቸው ህመም በሆስፒታል በሕክምና ላይ እንዳሉ ዛሬ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃ ያመላክታል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከአባታቸው ከአቶ ገብረሥላሴ ገ/መድኅንና ከእናታቸው ወይዘሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ልዩ ስሙ በዓታ ለማርያም በተባለ ቦታ በ1934 ዓ.ም ነበር የተወለዱት።