Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌደሬሽን ምክር ቤቶች 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ካነሷቸው ነቦች

👉 የተሰበረውን በመጠገን፣ ልዩነቶቸን በማጥበብ፣ የተጣመመውን በማቃናት እና ስህተቶችን በማረም ሀገርን በማይናወጥ መሰረት ልናፀና ይገባል፣

👉 ቆም ብለን የመጣንበትን መንገድ ገምገመን ያተረፍንበትን በማጠናከር የከሰርንበትን ደግሞ ማስተካከል ይኖርብናል፣

👉 ያደጉ የምንላቸው ሀገራት ዛሬ ላይ የደረሱት ልዩነት ሳይኖራቸው ቀርቶ ሳይሆን ልዩነታቸውን በውይይት መፍታት በመቻላቸው ነው፣

👉 ትላንት ለነገ ትምህርት እንጂ እንቅፋት ሊሆን አይገባም፣ የትናንት ታሪክ የአብሮነት መገንቢያ እንጂ የልነት መነሻ እንዳይሆን መስራት አለብን፣

👉 ባለፉት ዓመታት በፈተና እና በተለያዩ ተግዳሮቶች ውስጥ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጦች ተመዘግበዋል፣

👉 ኢኮኖሚያችን አዲስ የታሪክ እጥፋት ላይ ነው፣ ከነጠላ ዘርፍ ወደ ባለ ብዙ ዘርፍ አኮኖሚነት ተሸጋግሯል፣ ሀገራዊ የልማት ግቦችም በተያዘላቸው ጊዜ እየተከናወኑ ነው፣

👉 ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏብሔራዊ የዲፕሎማሲ ስኬት ሆኖ ተመዝግቧል፣

👉 ተነጋግረን ባንግባባም ጦርነት አማራጭ ሆኖ መቅረብ የለበትም፣ በጦርነት አንድ አሸናፊ ይኖራል፣ በውይይት ግን ሁሉም አሸናፊ ነው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.