አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕንድ በተካሄደው 18ኛው የደልሂ ግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር አትሌት አልማዝ አያና አሸነፈች፡፡
ርቀቱን ለማጠናቀቅም 1 ሰዓት ከ 7 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ፈጅቶባታል።
አትሌቷ ከረጅም ጊዜ ጉዳት በኋላ ወደ ዓለም አቀፍ ውድድር ተመልሳ ያስመዘገበችው ውጤት መሆኑ ተገልጿል፡፡
የ2016 የሪዮ ኦሎምፒክ አሸናፊዋ አትሌት አልማዝ አያና ከ6 ዓመታት በፊትም በደልሂ በተካሄደ ተመሳሳይ የግማሽ ማራቶን ውድድር ማሸነፏ ይታወሳል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!