የሀገር ውስጥ ዜና

የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን አቅም መገንባት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ወሳኝ ነው – ዶ/ር ሊያ ታደሰ

By Feven Bishaw

May 18, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ስለኮሮና ቫይረስ ስለቤት ለቤት ቅኝት እና አሰሳ እንዲሁም ወረርሽኙን ለመከላከል መኖር ያለበትን ቅንጅታዊ አሰራር በተመለከተ አቅማቸውን መገንባት ቫይረሱን ለመከላከል ወሳኝ ተግባር መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

ሚኒስትሯ የኮሮና ቫይረስ ወረረሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የተዘጋጀ በተንቀሳቃሽ ስልክ የሚሰጥ ስልጠና ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።