Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ምስጋኑ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጆሴ ማሲንጋ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትር ዴዔታው ለአምባሳደሩ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክታቸውን ካስተላለፉ በኋላ፥ ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን መድረኮች ላይ የሚያደርጉትን ትብብር አድንቀዋል።

የሀገራቱን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር እና የተቀናጀ ውይይትን ማደስ ያለውን አስተዋጽዖም አመላክተዋል።

አምባሳደር ምስጋኑ አክለውም፥ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላትን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እና የንግድ ግንኙነት ለማሳደግ ያላት ፍላጎትም ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

አምባሳደር ማሲንጋ በበኩላቸው፥ አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነቷ ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነትና ፍላጎት ማረጋገጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#Ethiopia #USA

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.