የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተፈጥሮ ጸጋና ሃብትን በማልማት ለዘላቂ ሰላምና ልማት ይሰራል ተባለ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የክልሉን የተፈጥሮ ጸጋና ሃብትን በማልማት በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ እንደሚሠራ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው ገለጹ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥረታ ማጠቃለያ መርሐ- ግብር በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡
አቶ እንደሻው ጣሰው በመርሐ- ግብሩ እንደተናገሩት÷ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዘርፈ ብዙ አቅም ያለው መሆኑን አንስተዋል፡፡
የክልሉ ሕዝቦች በአዲስ ምዕራፍ፣ በአዲስ ተስፋ፣ በጋራ እንደሚሠሩ ገልጸው÷ ሕዝቡ ሙሉ አቅሙን ለሰላም ግንባታና ልማት እንዲያውል ጠይቀዋል።
በበረከት ተካልኝ
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!