አቶ አወል አርባ በአዋሽ ፈንታሌ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝታቸውም በአካባቢው እየለማ የሚገኘውን የፓፓዬ ምርት እና ሌሎች ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
አቶ አወል በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት÷ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገው ጥረት አበረታች እንደሆነም በማህበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!