ስፓርት

ማንቼስተር ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል

By ዮሐንስ ደርበው

November 04, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ ከተከታታይ ሽንፈት በኋላ ፉልሃምን በማሸነፍ ወሳኝ ሦስት ነጥብ አሳክቷል፡፡

1 ለ 0 በተጠናቀቀው ጨዋታ ቡሩኖ ፈርናንዴዝ ብቸኛዋን የማሸነፊያ ጎል አስቆጥሯል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ጫና ውስጥ የነበሩት አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግ እፎይታን አግኝተዋል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድም ድሉን ተከትሎ ነጥቡን 18 በማድረስ ለጊዜው 6ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!