የሀገር ውስጥ ዜና

በ24 ሰዓት በተደረገ 3 ሺህ 747 የላብራቶሪ ምርመራ 9 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

By Tibebu Kebede

May 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3 ሺህ 747 የላብራቶሪ ምርመራ 9 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ይህንን ተከትሎም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 398 መድረሱን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታውቅዋል።