የሀገር ውስጥ ዜና

ከግብርና ምርቶች ከ600 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር  በላይ የውጪ ምንዛሪ ተገኘ

By Meseret Demissu

May 21, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2012  (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2012 በጀት ዓመት በ9 ወራት በግብርና ምርቶች ከ600 ሚሊየን  የአሜሪካን ዶላር በላይ የውጪ ምንዛሪ መገኘቱን ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ ÷ በበጀት ዓመቱ 9 ወራት 690ሺህ840 ቶን ምርት ለውጪ ገበያ በማቅረብ 818 ሚሊየን 611 ሺህ 770 ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 473 ሚሊየን 959 ሺህ 69 ቶን ምርት በመላክ 658 ሚሊየን 200 ሺህ 550 የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።