የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጋር በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ተወያዩ

By Tibebu Kebede

May 21, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ጋር በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ተወያዩ።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በቪዲዮ ኮንፍረንስ በተካሄደው ውይይት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በተጨማሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ጨምሮ የሁለቱም ሀገራት ከፍተኛ ልኡካን ተሳትፈዋል።