የሀገር ውስጥ ዜና

በከተማ ደረጃ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገቢ እና የህብረተሰብ ተሳትፎ ንቅናቄ ስራ ተጀመረ

By Feven Bishaw

May 22, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በከተማ አቀፍ ደረጃ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገቢ እና የህብረተሰብ ተሳትፎ ንቅናቄ ስራ ተጀመረ።

መርሃ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት አስተባባሪ እና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ኢንጅነር እንዳወቅ አብቴ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ኢትዮጵያ ከድህነት ለመላቀቅ የምታደርገውን ትግል እውን ማድረጊያ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።