Fana: At a Speed of Life!

የልጆችን በሽታ የመከላከል አቅም እንዴት መጨመር ይቻላል?

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ህጻናት በቀላሉ እንዳይታመሙ በሽታ የመከላከል አቅማቸው መጎልበት አለበት፡፡

ይህንንም ለማድረግ መሠረታዊ መርሆችን መከተል ይገባል፡፡

እነሱም፡-

-ጡት ማጥባት፡- ቢያንስ ለመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ጡት ብቻ ማጥባት የራሱ የሆኑ ጠቀሜታዎችን የሚሰጥ ሲሆን÷ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ጡት ማጥባት አለርጂ የመያዝ እድልን ይቀንሳል፡፡

– በየጊዜው እጅ መታጠብ፡- ልጆችን ሲያስነጥሱ፣ ሲያስሉ እና ወደ መጸዳጃ ቤት ከሄዱ በኋላ እጃቸውን ለመታጠብ ጊዜ እንዲወስዱ አስተምሯቸው።

– እጅን በሞቀ ውሃ እና ሳሙና ቢያንስ ለ20 ሰከንድ መታጠብ ባክቴሪያዎችን እና ቫይረሶችን ያስወግዳል፣ እስከ 45 በመቶ የሚደርስ የሳንባ ኢንፌክሽን እድልንም ይቀንሳል።

– የክትባት ወቅትን አለማሳለፍ፡- በልጅነት የሚወሰዱ ክትባቶች እንደ ኩፍኝ ፣ ጉድፍ፣ ፖሊዮ እና ሮታ ቫይረስን ስለሚከላከል የክትባት ጊዜ ፈጽሞ አያምልጣቸው፡፡

– አመጋገብን ማስተካል፡- ትክክለኛ የምግብ ምርጫ ልጅዎ በቂ ቫይታሚኖችን ማግኘቱን ለማረጋገጥ ይረዳል፤ ጤናን ለመጠበቅ እና ጠንካራ የበሽታ መከላከል ስርዓትን ለመጠበቅ ቫይታሚኖች ያስፈልጋሉ።

– በቂ እንቅልፍ ማግኘት፡- ልጆች በሽታ የመከላከል አቅማቸው ከፍ እንዲል በቂ እንቅልፍ ማግኘት ያለባቸው ሲሆን የእንቅልፍ ሰአቱ እንደ እድሜያቸው መጠን ይለያያል፡፡

በዚህም ከ0 እስከ 3 ወር ያሉ ህጻናት ከ14 እስከ 17 ሰአታት መተኛት ያስፈልጋቸዋል፤ ከ 4 እስከ 12 ወራት ውስጥ ያሉት ከ 12 እስከ 16 ሰአታት መተኛት ያስፈልጋቸዋል::

ከ 1 እስከ 2 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ልጆች ደግሞ ከ11 እስከ 14 ሰዓታት መተኛት ያስፈልጋቸዋል፤ ከ 3 እስከ 5 ዓመት እድሜ ያላቸው ልጆች ከ 10 እስከ 13 ሰአታት እንቅልፍ ማግኘት እንዳለባቸው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.