የኢትዮ-ጂቡቲ የመከላከያ ሚኒስቴር የጋራ ቴክኒካል ኮሚቴ ስብሰባ ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 10ኛው ዙር የኢትዮ-ጂቡቲ የመከላከያ ሚኒስቴር የጋራ ቴክኒካል ኮሚቴ ስብሰባ ዛሬ ተጀምሯል፡፡
በጂቡቲ እየተካሄደ በሚገኘው ስብሰባ ላይ ከኢትዮጵያ በኩል በብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ አናጋው የተመራ ልዑክ እየተሳተፈ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ከቴክኒካል ኮሚቴ ስብሰባው ጎን ለጎንም ብርጋዲየር ጄኔራል ተሾመ አናጋው ከጂቡቲ አቻቸው ብርጋዲየር ጄኔራል ጣሂር ዓሊ መሐመድ ጋር በጸጥታ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ስብሰባው ነገ ፍጻሜውን ያገኛል መባሉን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!