ዓለምአቀፋዊ ዜና

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለኮሮናቫይረስ ክትባት ስራ የተሰበሰበው ገንዘብ ከ10 ቢሊየን ዶላር አለፈ

By Tibebu Kebede

May 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዓለም ዙሪያ ለኮሮናቫይረስ ክትባት ለማግኘት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ እየተሰበሰበ ያለው ገንዘብ 10 ነጥብ 4 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር መድረሱን የአውሮፓ ህብረት ገለፀ።

ባሳለፍነው ወር በአውሮፓ ህብረት አስተባባሪነት ዓለም አቀፍ የኮሮና ክትባት የማፈላለግ ስራ የገንዘብ ድጋፍ ዘመቻ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።