የሀገር ውስጥ ዜና

በጋምቤላ ክልል የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ተጀመረ

By Tibebu Kebede

May 27, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል በቀን 180 የኮሮና ቫይረስ ናሙናዎችን መመርመር መጀመሩን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡሞድ ኡጁሉ እንዳሉት በሀገሪቱ የኮቪድ 19 መከሰቱ ከታወቀ ጀምሮ በጋምቤላ ክልል በርካታ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራ ሲከናወን ቆይቷል ብለዋል፡፡