ስፓርት

የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ሰኔ 10 ወደ ውድድር ሊመለስ ነው

By Tibebu Kebede

May 28, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ሰኔ 10 ቀን ወደ ውድድር ሊመለስ መሆኑ በዛሬው እለት ተገልጿል።

ፕሪምየር ሊጉ ማንችስተር ሲቲ ከአርሰናል እንዲሁም አስቶንቪላ ከ ሼፍልድ ዩናይትድ በሚያደርጓቸው ተስተካካይ ጨዋታዎች እንደሚጀምርም ታውቋል።