የሀገር ውስጥ ዜና

የአየር መንገዱ አውሮፕላን አብራሪዎች ማህበር ለኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል ግምቱ 1 ሚሊየን ብር የሚጠጋ የህክምና ግብዓት ድጋፍ አደረጉ

By Feven Bishaw

May 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አብራሪዎች ማህበር ለኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል ግምቱ 1 ሚሊየን ብር የሚጠጋ የህክምና ግብዓት ድጋፍ አደረጉ፡፡

የማህበሩ ሊቀመንበር ካፒቴን በረከት አባተ 400 የቀዶ ጥገና አልባሳትና የፕላስቲክ ቡትስ ጫማዎች፣ አይፓድና ላፕቶፖችን ጨምሮ ሌሎች የህክምና ግብዓቶችን ለሆስፒታሉ ዳይሬክተር ዶክተር ያሬድ አግደው አስረክበዋል፡፡