የሀገር ውስጥ ዜና

በድንበር በኩል የሚገቡ ሰዎችን ለመቆጣጠር ከፌደራል መንግስት እና ከፀጥታ አካለት ጋር እየሰሩ መሆኑን የሶማሌ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አስታወቁ

By Feven Bishaw

May 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከጎረቤት ሀገራት በድንበር በኩል የሚገቡ ሰዎችን ለመቆጣጠር ከፌደራል መንግስት እና ከፀጥታ አካለት ጋር እየሰሩ መሆኑን የሶማሌ እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አስታወቁ።

የሶሜሌ ክልል ምክትል ርእሰ መሰተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ በድንበር አካባቢ ያሉ መግቢያዎችን ለመዝጋት እና ቁጥጥሩን ለማጠናከር ስራዎች በጥብቅ እየተሰሩ ነው ብለዋል።