የሀገር ውስጥ ዜና

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የእስካሁን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

By Feven Bishaw

May 29, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ተከትሎ በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም ላይ የሚኒስትሮች ኮሚቴ፣ ከፓርላማ መርማሪ ቦርድ አባላት እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት መደረጉን አስታወቁ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከፓርላማ መርማሪ ቦርድ አባላት እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር የተደረገው ውይይት ፍሬያማ መሆኑንም በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረዋል።