አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ተከትሎ በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈፃፀም ላይ የሚኒስትሮች ኮሚቴ፣ ከፓርላማ መርማሪ ቦርድ አባላት እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት መደረጉን አስታወቁ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከፓርላማ መርማሪ ቦርድ አባላት እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር የተደረገው ውይይት ፍሬያማ መሆኑንም በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረዋል።