ፋና ስብስብ

ለገና በዓል ከታረደ በሬ ከ6 ግራም በላይ ወርቅ ተገኘ

By Meseret Awoke

January 06, 2024

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለገና በዓል ከታረደ በሬ 6 ነጥብ 11 ግራም ወርቅ መገኘቱ ተሰምቷል፡፡

በወላይታ ሶዶ ከተማ ለገና በዓል ቅርጫ ከታረደው በሬ ውስጥ ነው 6 ነጥብ 11 ግራም ወርቅ የተገኘው።

በወላይታ ባህል ለበዓል “አሞ” ወይም ቅርጫ ማረድ የተለመደ ሲሆን÷ ነገ ለሚከበረው የገና በዓል በታረደው የቅርጫ በሬ ውስጥም ወርቅ መገኘቱ ተገልጿል፡፡

የቅርጫ አባላቱ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት ፥ የተገኘው ወርቅ የገና በዓል ስጦታ ነው።

በማህሌት ኡኩሞ

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.) ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!