Fana: At a Speed of Life!

የሞተር ሳይክሎች እና ከባድ ተሸከርካሪዎች ክልከላ የተደረጉባቸው መንገዶች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሞተር ሳይክሎችና ከሁለት ቶን በላይ የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ የመይችሉባቸውን መንገዶችን  የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አደርጓል ።

መንግዶቹ ቦሌ – በኦሎምፒያ – መስቀል አደባባይ – ብሔራዊ ቤተ -መንግሥት  እንዲሁም አራት ኪሎ በሁለቱም አቅጣጫ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

በመሆኑም የሞተር ሳይክል እና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች  ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች ከታህሳስ 29 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ አውቀው ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ  የአዲስ አበባ ፖሊስ  አሳስቧል።

በመንግዶቹ ክልከላውን የሚገልፁ ምልክቶች መተከላቸውን ያስታወቀው ፖሊስ የተላለፈውን መልዕክት በማያከብሩ  አሽከርካሪዎች ላይ ህጋዊ  እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.