Fana: At a Speed of Life!

አፈርን በኮምፖስት የማበልፀግ ልምምዳችንን በተሻለ ሁኔታ ካዳበርን ሰፊ ጥቅም እናገኝበታለን – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አፈርን በኮምፖስት የማበልፀግ ልምምዳችንን በተሻለ ሁኔታ ካዳበርን ሰፊ ጥቅም ልናገኝበት እንችላለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስት ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷አፈርን በኮምፖስት ማበልፀግ በተለይም በከተማ ግብርና ሥራችን ይበልጥ ተጠቃሚ ያደርገናል ብለዋል።

ኮምፖስት የአፈርን ይዘት ያሻሽላል፤ ለጠንካራ የእፅዋት ስርዓት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፤ የእፅዋት እድገት እና የጤንነት ደረጃን ይጨምራል ሲሉም ገልጸዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.