የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ አራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ተመረቁ

By Feven Bishaw

May 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ሲገነቡ የነበሩ አራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ተመረቁ።

ከተመረቁት የመንገድ ፕሮጀክቶች ውስጥ 3ነጥብ3 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 30 ሜትር ስፋት ያለው ከአራብሳ ኮንዶሚኒየም—አያት ኮንዶሚኒየም እንዲሁም 2ነጥብ1 ኪሎ ሜትር እና 20 ሜትር ስፋት ያለው ከሲ.ኤም.ሲ—አያት የተገነቡት መንገዶች ይገኙበታል።