የሀገር ውስጥ ዜና

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ላይ ተፈጥሮ በነረው ክስተት በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ሃዘን ገለፀ

By Feven Bishaw

May 31, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባሳለፍነው ሃሙስ በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ላይ ተፈጥሮ በነበረው ክስተት በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ሃዘን ገለፀ፡፡

ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ግንቦት 20 ቀን 2012 ዓ/ም በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተሰማውን ሃዘን ገልፆ በአደጋው ሰለባ ለሆኑ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝቷል፡፡